|
ከ6 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርግ የወባና ትራኮማ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ዘመቻ በመካሄድ ላይ ነው
ከሚያዚያ 20 እስከ ሚያዚያ 26/2004 ዓ.ም የሚቆይ 8ኛ ዙር የወባና ትራኮማ ሳምንት ሰሞኑን በሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋ ሮቢት ከተማ ይፋ ተደርጓል፡፡ ዘመቻውን ይፋ ያደረጉት የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ ሲስተር ዘቢደሩ ዘውዴ እንዳሉት በአገራችን መከላከልን መሰረት ያደረገ የጤና ፖሊሲ ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ወዲህ በጤናው ዘርፍ አበረታች ለውጦች መጥተዋል፡፡ በ2020 ዓ.ም ወባ የህብረተሰቡ የጤና ችግር የማይሆንበት ደረጃ ለመድረስና የትራኮማን በሽታም ለመከላከል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው፡፡
|
|
ለመጨረሻ ግዜ የተሻሻለው እሮብ, 16 ግንቦት 2012 05:51 |
|
|
ባህር ዳር ዓለም ዓቀፍ የስብሰባ ማዕከል እንድትሆን ትኩረት ተሰጦ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
የአማራ ክልል ባህል ቱሪዝም እና ፓርኮች ልማት ቢሮ ባህርዳር ከቱሪስት መዳረሻነት ባለፈ አለም አቀፍ የስብሰባ መዕከል እንድትሆን ለማስቻል ትኩረትሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ ፡፡
|
|
ለመጨረሻ ግዜ የተሻሻለው ማክሰኞ, 15 ግንቦት 2012 06:50 |
|
ጠንካራ ጋብቻና ቤተሰብ ኤችአይ.ቪ/ኤድስን ለመከላከል የሚኖረው ሚና የጐላ መሆኑ ተጠቆመ
እፎይ የጋብቻና ቤተሰብ ማማከር አገልግሎት ከዲኬቲ ኢትዮጵያ አማራ ክልል ማስተባባሪያ ጋር በመተባበር ታህሣስ 14/2ዐዐ4 ዓ.ም “ ጠንካራ ጋብቻና ቤተሰብ ኤድስን ለመከላከል ያለው ሚና” በሚል በባህር ዳር ከተማ ኢትዮ ስታር ሆቴል የፖናል ውይይት አካሂዷል፡፡ የፖናል ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የአማራ ክልል ሴቶች ፌዴሬሽን ኃላፊ ወ/ሮ እመቤት ምትኩ እንደተናገሩት ጠንካራና በመተማመን ላይ የተመሰረተ ጋብቻ በኤች.አይ.ቪ የመያዝ ዕድልን አናሣ ያደርገዋል፡፡ ባንፃሩ ደግሞ ጋብቻና ቤተሰብ በላላ ቁጥር ፍቺ ይከሰታል፤ ይህም ለኤድስ የመጋለጥ ዕድሉልን ያሰፋዋል፡፡ በመሆኑም አስተማማኝና ጠንካራ ጋብቻና ቤተሰብ በመመስረት በኤድስና ሌሎች ችግሮች የመጋለጥ ሁኔታን መቀነስ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
|
|
ለመጨረሻ ግዜ የተሻሻለው ማክሰኞ, 15 ግንቦት 2012 06:55 |
|
|